Laissez-passer (የይለፍ ሰነድ)
ሊሴ ፓሴ መግቢያ የጉዞ ሰነድ ለሚጠይቁ
- ለአስቸካይ ጉዞ ወደ አገር ቤት ለመሄድ የአገልግሎት ጊዜውን ያበቃ ፓስፖርት ለማሳደስ በቂ ጊዜ የሌላቸው በተለያየ አስቸኳይ ምክንያት ወደ አገርቤት ለመጓዝ የፈለጉ ሌሴ ፓሴ መጠየቅ።
- ሊሴ ፓሴው ለአንድ ጊዜ ወደ ኢትዮጵያ መግቢያ ብቻ የሚያገለግል በመሆኑ ሲመለሱ ከኢትዮጵያ ፓስፖርት ማውጣት እንደሚጠበቅ።
- የፓስፖርትና የሊሴ ፓሴ ማመልከቻ በአንድ ላይ ማቅረብ ወይም የፓስፖርትዎ ማመልከቻ ከኤምባሲው ወደ አገር ቤት ከተላከ ከአንድ ወርና ከዚያ በላይ ሳይሆን ሊሴ ፓሴ ማመልከት አይቻልም። ነገር ግን ኢምባሲው ማመልከቻዎን አገር ቤት ከተላከ አንድ ወርና ከዚያ በላይ ከሆነና ፓስፖርቱን ሳይረከቡ የጉዞዎ ቀን ከደረሰ ሊሴ ፓሴ ወስደው አገር ቤት ሲደርሱ የከፈሉበትን ደረሰኝ ይዞው ፓስፖርት ከኢሚግሬሽን መረከብ የሚችሉ መሆኑን።
- ባለጉዳዮች መላኪያም ሆነ መመለሻ ፖስታ መጠቀም የሚኖርባችሁ Tracking Number ባለው DHL TNT BPOST EXPRESS MAIL መሆን ይገባዋል፡፡ የላኩት ፖስታ ወደ ኤምባሲያችን ለመድረሱም ሆነ የተዘጋጀለዎት ሰነድ ወደ እርሶ ተመላሽ ለመደረጉ ባለዎት የፖስታ Tracking Number በመጠቀም ማጣራት ሰለሚችሉ ይህንኑ መረጃ ለማረጋገጥ ወደ ኢምባሲው መደወል አይጠበቅም።
መሟላት የሚገባቸው መስፈርቶች
- ሁለት (2) የፓስፖርት መጠን ያለውና ቢያንስ ከ6ወር ወዲህ የተነሱት ፎቶግራፍ (ሁለቱ ጆሮ የሚታይ፣ መደቡ ነጣያለና ከጀርባው ስም የተጻፈበት)
- አገልግሎቱ ያበቃዉን ፓስፖርት መረጃ ያለበትን ማለትም ስም፣ ፎቶግራፍ፣ ፓስፖርቱ የተሰጠበትና ለመጨረሻ ጊዜ የታደሰበትን ገጽ የሚያሳይ ኮፒ ማቅረብ
- በቤኔሉክስ አገሮችየሚኖሩበትን ስታተስ የሚያሳይ የመኖሪያ ፍቃድ ወይም የስራ ፍቃድ ማስረጃ ኮፒ ማቅርብ ፣
- የአገልግሎት ክፍያ 117.60 ዮሮ ለኢትዮጵያ ኤምባሲ አካውንት BANK ACCOUNT IBAN: BE53 3631 2148 4153 ማስገባት
- የሊሴ ፓሴ መጠየቂያ ቅጽ መሙላት Laissez-passer Form
- የተለየ ችግር ያለባቸው አድራሻዎ የተጻፈበት መመለሻ ፓስታ Tracking Number ያለው DHL TNT BPOST EXPRESS መላክ ይጠበቃል ፣ አሸራ መስጠት የሚጠበቅባቸው ማስረጃ ይዞው በግንባር መቅርብ ይገባል ፣
Latest News
- H.E. Ambassador Eshete Tilahun confers with the Honorable Dr. Hab. Marcin Czepelak ========================================== Today on the 20th October 2025, Ambassador Eshete Tilahun conferred with Dr. Czepelak, Secretary-General of the Permanent Court of Arbitration (PCA). During...
- The Embassy Ethiopia hosted the coordination meeting of East African Region ====================== The Embassy of Ethiopia in Brussels today convened the meeting of the East African Region Group of Ambassadors. Ambassador Eshete Tilahun chaired the...
- የኢትዮጵያ ዲፕሎማሲ ቀን በብራሰልስ የኢ.ፌ.ዲ.ሪ. ኤምባሲ በድምቀት ተከበረOctober 15, 2025የኢትዮጵያ ዲፕሎማሲ ቀን በብራሰልስ የኢ.ፌ.ዲ.ሪ. ኤምባሲ በድምቀት ተከበረ የኢትዮጵያ ዲፕሎማሲ ቀን በብራሰልስ የኢ.ፌ.ዲ.ሪ. ኤምባሲ ዲፕሎማቶች፣ ቤተሰቦቻቸው እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት ዛሬ ጥቅምት 4 ቀን 2018 ዓ.ም. በድምቀት ተከብሯል። እለቱን በማስመልከት ክቡር አምባሳደር እሸቴ ጥላሁን...
- 18ኛው የሰንደቅ አላማ ቀን በዓል በብራሰልስ የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ኤምባሲ በድምቀት ተከበረ፣October 13, 202518ኛው የሰንደቅ አላማ ቀን በዓል በብራሰልስ የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ኤምባሲ በድምቀት ተከበረ፣ _________________________________________________________________ በብራሰልስ የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ኤምባሲ ባልደረቦች በአገር አቀፍ ደረጃ ለ18ኛ ጊዜ “ሰንደቅ አላማችን ለኢትዮጵያ ታላቅ የከፍታ ብስራት፣ ለብሄራዊ አንድነታችን፣ ለሉዓላዊነታችንና ለኢትዮጵያ ህዳሴ’’ በሚል መሪ ቃል የሰንደቅ...
- The Ethiopian Delegation at the 16th AU– EU Annual Joint Peace & Security Consultative MeetingOctober 11, 2025The Ethiopian Delegation at the 16th AU– EU Annual Joint Peace & Security Consultative Meeting —————————————————————– A delegation led by Ambassador Hirut Zemene, Permanent Representative of Ethiopia to the African Union and the UNECA took...