የወሳኝ ኩነት ምዝገባ አፈጻጸም መመሪያ (የልደት፣ጋብቻ፣ፍቺ እና ሞት) የምስክር ወረቀት
በኢትዮጵያ ኤምባሲ ብራስልስ የወሳኝ ኩነት አገልግሎት ለመስጠት የሚያስፈልጉ ቅድመ ሁኔታዎች፣
መስፈርቶች እና ደጋፊ ማስረጃዎች፣
1. የልደት ምዝገባ
የልደት ምዝገባ ለማከናወን መሟላት የሚገባቸው ደጋፊ ማስረጃዎች እና መስፈርቶች፡-
1.1. አስመዝጋቢው ጊዜው ያላለፈበት የነዋሪነት/ብሄራዊ መታወቂያ ወይም ፓስፖርት ወይም የመኖሪያ ፍቃድ ወይም ስደተኝነቱን የሚገልጽ ማስረጃ ማቅረብ አለበት።
1.2. በውጭ ለሚኖሩ ኢትዮጵያዊያን ልደቱ የተከሰተው በጤና ተቋም ከሆነ አስመዝጋቢው ከጤና ተቋም የተሰጠውን የልደት ማስረጃ ማቅረብ አለበት።
1.3. የልደት አስመዝጋቢው ከጤና ተቋም የተሰጠውን የልደት ማሳወቂያ ቅጽ ማቅረብ አለበት፡፡ ሆኖም ምዝገባው ከመጀመሩ በፊት የተከሰተን ልደት ምዝገባን አይጨምርም።
1.4. የህጻኑ አሳዳጊ ወይም ተንከባካቢ ልደቱን ለማስመዝገብ ሕጋዊ የአሳዳሪነት ወይም ተንከባካቢነት ማስረጃ ማቅረብ አለባቸው።
1.5. ዕድሜው አስራ ስምንት ዓመትና በላይ የሆነ ስደተኛ ወላጆቹን የሚገልፅ ማስረጃ ከስደተኞች መረጃ ዳታ ቤዝ ላይ መረጃው የሌለ እንደሆነ ስደተኛውን በመጠየቅ መመዝገብ አለበት።
1.6. የልደት ምዝገባ አገልግሎት ክፍያ 53.10 ዩሮ ብቻ ነው።
2. የጋብቻ ምዝገባ
የጋብቻ ምዝገባ ለማከናወን መሟለት የሚገባቸው ደጋፊ ማስረጃዎች እና መስፈረቶች፡-
2.1. ተጋቢዎች ጋብቻ ለመፈፀም ማሰባቸውን እጅግ ቢዘገይ ጋብቻቸውን ለመፈፀም ከወሰኑበት ቀን ከአንድ ወር በፊት ለኢምባሲው ማስታወቅ አለባቸው፡፡ሆኖም ይህ ድንጋጌ በሃይማኖታዊ እና ባህላዊ ስርዓት የሚፈፀም ጋብቻን አይመለከትም።
2.2. የክብር መዝገብ ሹሙ ጥያቄው በቀረበለት ቀን ከተጋቢዎቹ ጋር በመነጋገር ከወሰነ በኃላ በማግስቱ ጋብቻው የሚፈፀምበትን ቀን በመግለጽ አመቺ በሆነው መንገድ ለ15 ተከታታይ ቀን የሚቆይ ማስታወቂያ ያወጣል።
2.3. ተጋቢዎች ማንነታቸውን የሚገልጽ ማስረጃ ማቅረብ አለባቸው።
2.4. የተጋቢ ምስክሮች አገልግሎቱ ያላለፈበት የነዋሪነት/ብሄራዊ መታወቂያ ወይም የስደተኝነት መታወቂያ ወይም ፓስፖርት ወይም ሌላ ማንነትን ሊገልፅ የሚችል ማስረጃ መቅረብ አለበት።
2.5. ተጋቢዎች ከዚህ በፊት አግብተው የተፋቱ ከሆነ የፍቺ ምስክር ወረቀት ካለ መቅረብ አለባቸው።
2.6. ከ 6 ወር ወዲህ በተመሳሳይ ጊዜ የተነሱት ሁለት ሁለት 3 በ 4 የሆነ የተጋቢዎች ፎቶ-ግራፍ መቅረብ አለበት።
2.7. በባህላዊ ስርዓት የተፈፀመ ጋብቻ የተጋቢዎች ምስክሮች ወይም በጋብቻ ስርዓቱ ላይ የታደመ ሰው በክብር መዝገብ ሹሙ ፊት በአካል ቀርበው ፊርማቸውን ማኖር አለባቸው።
2.8. የተጋቢዎች የልደት ምስክር ወረቀት ካለ መቅረብ አለበት።
2.9. በሙሽራው በኩል 2 በሙሽሪት በኩል 2 በድምሩ 4 ምስክሮች መቅረብ አለባቸው፡፡ሆኖም በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ 16 መሰረት የተፈፀመ ከሆነ ምስክሮችን በተመለከተ ያለው ክፍት ቦታ በሰረዝ (-) ይታለፋል።
2.10. ተጋቢው ስደተኛ ከሆነ የስደተኝነት እውቅና ያገኘ መሆን አለበት፡፡በማንኛውም ስርዓት የሚፈፀም ጋብቻ ከዚህ በላይ የተዘረዘሩ ቅድመ ሁኔታዎችን ማሟላት አለበት።
2.11. የጋብቻ ምዝገባ አገልግሎት ክፍያ 53.10 ዩሮ ብቻ ነው።
3. የፍቺ ምዝገባ
የፍቺ ምዝገባ ለማከናወን መሟላት የሚገባቸው ቅድመ ሁኔታዎችና ደጋፊ ማስረጃዎች፡-
3.1. ፍቺው ስልጣን ባለው ፍርድ ቤት የተፈፀመ መሆን አለበት።
3.2. የፍቺ አስመዝጋቢ ሆነው የሚቀርቡት ተፋቺዎች በጋራ ወይም ከተፋቺዎች አንዱ ወይም የተፋቺዎች ልዩ ውክልና ያለው መሆን አለበት።
3.3. ተፋቺው ስደተኛ ከሆነ የስደተኝነት እውቅና ያገኘ መሆን አለበት።
3.4. ፍቺው በፍርድ ቤት የተከናወነ መሆኑን የሚገልፅ የፍርድ ቤት ውሳኔ ግልባጭ መቅረብ አለበት።
3.5. ተፋቺዎች ፍቺውን ለማስመዝገብ ሲመጡ ጊዜው ያላለፈበት የመኖሪያ ፈቃድ ወይም ፓስፖርት ወይም ማህበራዊ መታወቂያ ወይም ስደተኝነታቸውን የሚገልጽ ማስረጃ ማቅረብ አለባቸው።
3.6. ቀደም ሲል የጋብቻ ምስክር ወረቀት የተሰጠ ከሆነ መመለስ አለበት።
3.7. የፍቺ ምዝገባ አገልግሎት ክፍያ 53.10 ዩሮ ብቻ ነው።
4. የሞት ምዝገባ
የሞት ምዝገባ ለማከናወን የሚያስፈልጉ ደጋፊ ማስረጃዎች፡-
4.1. ሞቱን ለማስመዝገብ ከጤና ተቋም የተሰጠ ማስረጃ መቅረብ አለበት።
4.2. የሟች ማንነት የሚገልጽ ማሰረጃ ወይም የመኖሪያ ፈቃድ ወይም ፓስፖርት ወይም ሊሴ-ፓሴ ወይም ማህበራዊ መታወቂያ መቅረብ አለበት።
4.3. የሞት አስመዝጋቢ ከሀገሩ መንግሥት የሞት ምስክር ወረቀት ይዞ መቅረብ አለበት።
4.4. ሞቱ የሚመዘገበው በግለሰቡ መጥፋት ውሳኔ ምክንያት ከሆነ የፍርድ ቤት ውሳኔ ትክክለኛ ግልባጭ መቅረብ አለበት።
4.5. የሞት ምዝገባ አገልግሎት ክፍያ 53.10 ዩሮ ብቻ ነው።
Latest News
- H.E. Ambassador Eshete Tilahun confers with the Honorable Dr. Hab. Marcin Czepelak ========================================== Today on the 20th October 2025, Ambassador Eshete Tilahun conferred with Dr. Czepelak, Secretary-General of the Permanent Court of Arbitration (PCA). During...
- The Embassy Ethiopia hosted the coordination meeting of East African Region ====================== The Embassy of Ethiopia in Brussels today convened the meeting of the East African Region Group of Ambassadors. Ambassador Eshete Tilahun chaired the...
- የኢትዮጵያ ዲፕሎማሲ ቀን በብራሰልስ የኢ.ፌ.ዲ.ሪ. ኤምባሲ በድምቀት ተከበረOctober 15, 2025የኢትዮጵያ ዲፕሎማሲ ቀን በብራሰልስ የኢ.ፌ.ዲ.ሪ. ኤምባሲ በድምቀት ተከበረ የኢትዮጵያ ዲፕሎማሲ ቀን በብራሰልስ የኢ.ፌ.ዲ.ሪ. ኤምባሲ ዲፕሎማቶች፣ ቤተሰቦቻቸው እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት ዛሬ ጥቅምት 4 ቀን 2018 ዓ.ም. በድምቀት ተከብሯል። እለቱን በማስመልከት ክቡር አምባሳደር እሸቴ ጥላሁን...
- 18ኛው የሰንደቅ አላማ ቀን በዓል በብራሰልስ የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ኤምባሲ በድምቀት ተከበረ፣October 13, 202518ኛው የሰንደቅ አላማ ቀን በዓል በብራሰልስ የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ኤምባሲ በድምቀት ተከበረ፣ _________________________________________________________________ በብራሰልስ የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ኤምባሲ ባልደረቦች በአገር አቀፍ ደረጃ ለ18ኛ ጊዜ “ሰንደቅ አላማችን ለኢትዮጵያ ታላቅ የከፍታ ብስራት፣ ለብሄራዊ አንድነታችን፣ ለሉዓላዊነታችንና ለኢትዮጵያ ህዳሴ’’ በሚል መሪ ቃል የሰንደቅ...
- The Ethiopian Delegation at the 16th AU– EU Annual Joint Peace & Security Consultative MeetingOctober 11, 2025The Ethiopian Delegation at the 16th AU– EU Annual Joint Peace & Security Consultative Meeting —————————————————————– A delegation led by Ambassador Hirut Zemene, Permanent Representative of Ethiopia to the African Union and the UNECA took...