Category: News

embassy news

የኢትዮጵያ፣ ሱዳን እና ግብጽ የውሃ ጉዳይ ሚኒስትሮች በታላቁ የሕዳሴ ግድብ ሙሌት እና ውሃ አለቃቅ ላይ ያካሄዱት የቴክኒክ ስብሰባ ተጠናቀቀ

 

በታላቁ የኢትዮጵያ የህዳሴ ግድብ ሙሌት እና የውሃ አለቃቅ ላይ ለሁለት ቀናት በአደስ አበባ ሲካሄድ የቆየው የውሃ ሚኒስትሮች ቴክኒካል ስብሰባ ዛሬ ታህስስ 30 ቀን 2012 ዓም ተጠናቋል፡፡

ስብሰባው የውሃ ሚኒስትሮቹ እ.ኤ.አ ከኖቬምበር 06 ቀን 2019 ወዲህ የተደረገ አራተኛ የሚኒስትሮች ቴክኒካል ስብሰባ ነው፡፡ ስብሰባዎቹ የሶስቱ ሀገራት መሪዎች እ.ኤ.አ 10 ፌብሩዋሪ 2019 አዲስ አበባ ባካሄዱት ስብሰባ የውሃ ጉዳይ ሚኒስትሮቻቸው የቴክኒክ ምክክሮችን በማድረግ በህዳሴ ግድብ ሙሌት እና አለቃቀቅ ጉዳይ ላይ አማራጭ ሃሳቦችን እንዲያቀርቡ በሰጡት መመሪያ መሰረት የተከናወነ የመጨረሻው ስብሰባ ነው፡፡

በስብሳባው የዝቅተኛ ውሃ አለቃቅ መጠን እና የድርቅ እና የተራዘመ ድርቅ ወቅት የሚኖረውን ትብብር ጨምሮ የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የውሃ አሞላል እና አለቃቀቅን የሚመለከቱ ቀሪ ጉዳዮች ላይ መግባባት ላይ ይደረሳል ተብሎ የተጠበቀ ቢሆንም ስብሰባው ያለስምምነት ተጠናቋል፡፡

ኢትዮጵያ ወንዙ በግድቡ ስፍራ እንደሚኖረው ዓመታዊ የፍሰት መጠን ከ4 – 7 አመታትን በሚወስድ የሙሌት ደረጃ ግድቡን ለመሙላት፣ በሙሌት እንዲሁም ግድቡ ሙሌት አጠናቆ ስራ ከጀመረ በኋላም ድርቅ ከተከሰተ የማቃለያ እርምጃዎችን ለመውሰድ ሃሳቦችን አቅርባለች፡፡

እነዚህ ሃሳቦች የታችኛው ሀገራት ላይ ጉልህ ጉዳት እዳይደርስ የሚያስችሉ እንዲሁም ግብጽ እና ሱዳን ያቀረቧቸውን ሃሳቦች ያካተቱ ቢሆንም የግብጽ ወገን ያቀረብኩት ሃሳብ በሙሉ ተግባራዊ ካልሆነ የሚል አቋሙን ሳይንሳዊ ማስረጃ ቢቀርብለትም ሊቀበል ባለመቻሉ የቴክኒክ ውይይቱ ያለስምምነት ተጠናቋል፡፡

የግብጽ ወገን በዚህ ስብሰባ ያቀረበው ሃሳብ ኢትዮጵያ ከ12 – 21 አመታት ውስጥ ግድቡን እንድትሞላ እንዲሁም ከመጀመሪያው ሙሌት በኋላ ኢትዮጵያ ለምትጠቀመው ውሃ ለግብጽ የተጠራቀመ የውሃ ጉድለት ማካካሻ እንድትሰጥ የሚያስገድድ ነው፡፡ የኢትዮጵያ የግድብ አሞላል እና አለቃቀቅ ዕቅድ ድርቅን ከግምት ያስገባ ሆኖ እያለ የተጠራቀመ የውሃ ጉድለት የሚል ሃሳብ መነሳቱ ተገቢ አይደለም፡፡ በተጨማሪም የግብጽ ሃሳብ በናይል ወንዝ ላይ ተፈጥሯዊ ወይም ምንም ዓይነት የውሃ ልማት ያልተገነባበት ፍሰት እንዳለ የሚገምት እና ኢትዮጵያ ላለፉት 50 ዓመታት በላይ በጥቁር አባይ ወንዝ ላይ የሰራቻቸው የውሃ ልማት ስራዎች እንዳልተገነቡ የሚቆጥር ወይም እውቅና የሚነፍግ ነው፡፡

የግብጽ ሃሳብ ግብጽ በተፋሰሱ ላይ አለኝ የምትለውን የብቸኛ የውሃ ባለቤትነት ለማስጠበቅ የሚጥር ነው፡፡ ይህ አቋም በርትዕ እና ምክንያታዊነት ላይ የተመሰረተ የውሃ አጠቃቀም እና በትብብር መስራት መርሆዎችን የሚጥስ ነው፡፡ እነዚህ እንዲሁም ጉልህ ጉዳት ያለማድረስ መሰረታዊ መርህ ግብጽ፣ ሱዳን እና ሀገራችን በመሪዎች ደረጃ መጋቢት 2007 ዓ.ም ላይ በካርቱም በፈረሙት በታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የመርሆዎች መግለጫ ስምምነት ውስጥ የተካተቱ መሆናቸው ይታወቃል፡፡

የአባይ/ናይል ወንዝ አጠቃቀም ለኢትዮጵያ የህልውና ጉዳይ በመሆኑ ኢትዮጵያ በናይል ወንዝ የመጠቀም ሉዓላዊ መብቷን የማስከበርና የነባሩን እንዲሁም የመጪውን ትውልዶች የመጠቀም መብት የማረጋገጥ ጥረቷን አጠናክራ ትቀጥልበታለች፡፡ ኢትዮጵያ በናይል ወንዝ ላይ ለተፈረሙ እና አባል ላልሆነችባቸው የቅኝ ግዛት እና ድህረ ቅኝ ግዛት ኢፍትሐዊ እና አግላይ እንዲሁም ለናይል ወንዝ 77 ቢሊየን ሜትር ኪዩብ ውሃ ለምታዋጣው ኢትዮጵያ 0 ድርሻ ለሚሰጡ “ውሎች” እውቅና እንድትሰጥ የሚደረጉ ሙከራዎችን አትቀበልም፡፡ በተጨማሪም ሀገራችን ከተፋሰሱ ሀገራት ጋር በምታደርገው ውይይት የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የትብብር እና የጋራ ልማት ምሳሌ እንዲሆን በወንድማማችነት፣ በቅን ልቦና እና በመተባበር መንፈስ ጥረቷን ትቀጥላለች፡፡

በቀጣይ የውሃ ሚኒስትሮቹ የተስማሙባቸው እና ልዩነት የተመዘገበባቸው ጉዳዮች ተለይተው ለመሪዎች የሚቀርቡ ሲሆን መሪዎች ስለቀጣይ እርምጃ አቅጣጫ እንደሚያስቀምጡ ይጠበቃል፡፡

የታላቁ ህዳሴ ግድብን የውሃ አሞላል እና አለቃቀቅ የሚመለከቱ ሁሉም ቴክኒካዊ ጉዳዮች በሳይንሳዊ መረጃ ላይ የተመሰረተ ውይይት ተደርጎባቸዋል፡፡ ሀገራቱ ሙሌት እና አለቃቀቅን የሚመለከቱ ጉዳዮች ላይ የሃሳብ መቀራረብ አሳይተዋል፡፡ ሁሉም ሀገራቱ በውይይቱ የሚያደርጉት ተሳትፎ በቀናነት እና የትብብር መንፈስ ከተከናወነ የሚኒስትሮች ስብሰባዎቹ ሀገራቱ በራሳቸው መካከል በሚደረግ ውይይት ስምምነት ለመድረስ ያላቸውን እድሎች ያሳየ መሆኑን ኢትዮጵያ ታምናለች፡፡

የውሃ ሚኒስትሮቹ እ.ኤ.አ ጃኑዋሪ 13 ቀን 2020 በዋሽንግተን ዲሲ የሚገናኙ ሲሆን ስብሰባው እስካሁን የተደረጉ የቴክኒክ ምክክርች ሂደት የሚገመገምበት ብቻ ይሆናል፡፡

7ኛው የኢትዮጵያ፣ የግብፅና የሱዳን የውሃ ጉዳይ የሚኒስትሮች ስብሰባ ተጀመረ

በታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የውሃ ሙሌትና አለቃቀቅ ጉዳይ ላይ የሚመክረው የመጨረሻው የኢትዮጵያ፣ የሱዳንና የግብፅ የውሃ ጉዳይ ሚኒስትሮች የቴክኒክ ስብሰባ ዛሬ ታህሳስ 29 ቀን 2012 ዓ.ም. በአዲሰ አበባ መካሄድ ተጀምሯል፡፡

የዛሬው ስብሰባ በዋናነት የግድቡ የውኃ ሙሌትና አለቃቀቅን በሚመለከት ውይይት ያደርጋል፡፡

በስብሰባው የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት ክቡር የውሃ፣ መስኖ እና ኢነርጂ ሚኒስትር ዶ/ር ስለሺ በቀለ የአባይ ውሃ ለኢትዮጵያ ድህነትን ማጥፊያ እና የህልውና ጉዳይ መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡ ክቡር ሚኒስትሩ ስብሰባው በግድቡ ሙሌት እና የውኃ አለቃቅ ዙሪያ ውይይት በማድረግ መግባባት ላይ እንደሚደረስ ተስፋቸውን በመጠቆም ሚኒስትሮቹ በሶስቱ ሀገራት ዘንድ በጉጉት ለሚጠብቁት ህዝቦች መልካም ዜና ለማብሰር ውይይቱን በሰከነና በመግባባት መንፈስ በማካሄድ መቋጨት እንደሚጠበቅባቸው ገልጸዋል፡፡ ለዚሁም መሠረቱ የመሪዎች መግለጫ፣ የወንዙን ውኃ ምክንያታዊ አጠቃቀም እና ጉልህ ጉዳት ባለማድረስ መርህ እንደሆነም ዶ/ር ስለሽ ጠቁመዋል፡፡

የግብጽ እና የሱዳን የውሃ ሚኒስትሮችም በስብሰባው መክፈቻ ንግግር ያደረጉ ሲሆን በትብብር መንፈስ በአጀንዳዎቹ ዙሪያ ውይይት እንደሚደረግና የጋራ መግባባት ላይ እንደሚደረስ ያላቸውን ተስፋ ገልጸዋል፡፡
በስብሰባው የዓለም ባንክ እና የአሜሪካ መንግሥት ተወካዮች በታዛቢነት ተገኝተዋል፡፡

President Sahle-Work Visits Unity Park

Located in the Palace of Menelik ll, Unity Park was inaugurated and opened for visitors last October. President Sahle-work Zewde who then attended the inauguration of the Park was back again after a little more than three months.
During her visit, the President said it is important to understand history in order to understand the present and shape the future.

Ethiopia Launches e-platform

Ethiopia on Saturday launched the Electronic Single Window (eSW) platform, a one-stop service system, to facilitate the import and export trade.

The Project (eSW), which was officially launched by Prime Minister Abiy Ahmed will help improving “Ease of doing Business” in Ethiopia.

“By creating a paperless environment, eliminating multiple physical inspections and repetitive document submissions, the Electronic Single Window Project will reduce clearance time from 44 days to three days,” it was noted.

Moreover, the eSW platform is expected to reduce corruption through curtailing the possibility for corporal interaction.

Ethiopian Embassy Takes Part in an Annual Tourism Fair in Leuven, Belgium


This 5th of January 2020, the Embassy of Ethiopia in Brussels takes part in the HOBO Reizen anual tourism fair which takes place in Leuven, a town located 30 km from Brussels.
Organized by HOBO Reizen, a Belgian tour operator which includes Ethiopia in its tour packages, the one-day event attracted over 3,000 visitors. Among the tourist destinations displayed in the fair, a booth was separately arranged by the organizer to exhibit Ethiopia’s historical, cultural, and natural tourist attractions and provide information and explanations to the visitors.
The Embassy, in addition to providing information (orally, brochures, and video display) for the visitors, also hosted a traditional Ethiopian cultural coffee ceremony which caught the attention of many visitors, who had the occasion to enjoy some freshly-brewed Ethiopian Coffee and learn more about Ethiopia’s tourist destinations.

Joint task force established to tackle FDI challenges

The Ministry of Foreign Affairs said a joint forum led by Ambassador Girma Biru, macroeconomic advisor to Prime Minister Abiy Ahmed, was established with a specific task of tackling challenges of attracting Foreign Direct Investment (FDI) in Ethiopia.

Speaking at the opening of a panel organized by the Minister of Foreign Affairs, Foreign Minister Gedu Andargachew said that although the number of foreign investors willing to invest in Ethiopia has increased as of late, there is a wide gap that needs to be bridged in the proper handling of the inflow and overseeing the proper implementation of the sector.

Ambassador Girma Biru on his part said that it was essential to develop the country’s capacity to tackle implementation problems and highlighted the need to establish an organized forum dedicated to cascade the needs and strategies based on the types of problems investors are facing in the country.

Accordingly, the panel at the Ministry of Foreign Affairs agreed to establish a joint forum comprised of relevant stakeholders and to be led by Ambassador Girma Biru. The forum’s next meeting is scheduled to take place in the first week of February 2020.

The panel was attended by senior government officials, including Ahmed Shide, Finance minister and his deputy Eyob Tekalign; Abebe Abebayehu, commissioner, investment commission; as well as officials from the banking sector, including Yinager Dessie, the governor of National Bank of Ethiopia (NBE), and Teklewold Atnafu, former governor of NBE. In addition Ambassador Girma Biru and other experts from the Ministry of Mines and Energy, Ministry of Water and Irrigation, Ministry of Agriculture and other officials from the sector.

House Approves Anti-Terrorism Draft Bill

The House of Peoples Representatives of Ethiopia (HPR) today approved the anti-terrorism draft bill.

It endorsed the bill, which was drafted by the Attorney General and forwarded to it by the Council of Ministers, in majority vote with one abstention.

It was noted that the law would help prevent and control terrorism, protect the country from threats of terrorism and fill the gaps in the previous law.

The House will deliberate and refer to pertinent Standing Committee the bill drafted to approve the deal signed between Ethiopian and Qatar for investment promotion and protection.

It will also review and send to relevant bodies the draft bill to approve the Marrakesh Treaty to facilitate access to published works for persons who are blind, visually impaired and print disabled.

Moreover, the House will discuss on Protocol to the African Charter on Human and Peoples’ Rights on the Rights of Older Persons and the African Union Convention for the Protection and Assistance of Internally Displaced Persons in Africa (Kampala Convention).

በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የሴቶች፣ ህጻናትና ወጣቶች ጉዳይ ጽ/ቤት አማካኝነት በቤልጅዬም የአ.ፌ.ዴ.ሪ. ኤምባሲ ስልጠና እየተካሄደ ነው።

በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የሴቶች፣ ህጻናትና ወጣቶች ጉዳይ ጽ/ቤት አማካኝነት በጽ/ቤቱ ተግባርና ኃላፊነት፣ በጉዲፈቻ ህጻናት እቅድ አፈጻጸም እንዲሁም በአገራችን የህጻናት ድጋፍ ፕሮግራሞች ያተኮራ የሁለት ቀን ስልጠና ብራሰልስ በሚገኘው የኢ.ፌ.ዴ.ሪ. ኤምባሲ መሰጠት ጀመረ።

ስልጠናው በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የሴቶች፣ ህጻናትና ወጣቶች ጉዳይ ጽ/ቤት የተዘጋጅ ሲሆን፣ ከብራሰልስ፣ስቶኮልም፣ በርሊን እና ፍራንክፈርት የኢ.ፌ.ዴ.ሪ. ኤምባሲዎችና ቆንስል ጄኔራል ለተውጣጡ ዲፕሎማቶች የስልጠናው ተሳታፊዎች ናቸው።

Financial Times Named PM Abiy among 50 People of the Decade List

Prime Minister Abiy Ahmed has been selected as one of Financial Time’s top 50 persons who shaped the last decade.

Financial Times (FT) released a list of top 50 people who shaped the last decade where it had only listed one African, Prime Minister Abiy Ahmed.

The FT’s 50 People of the Decade reflects multi-dimensional developments, with game-changing politician and influential executives from banking and industry.

Prime Minister Abiy was listed under the politics category along with others including U.S. President Donald Trump, Chinese President Xi Jingping, German Chancellor Angela Merkel former U.S. president Barack Obama and Turkish President Recep Tayyip Erdogan.

Abiy received accolades for his domestic reform and initiating peace with Eritrea, which primarily brought him to the 2019 Nobel Peace Prize award.

The list is described as: “The game-changing politicians, influential business people, record-breaking sports stars and brave activists…”

The second decade of the 21st century began with austerity measures to deal with the downturn caused by the global financial crisis and ended with populist governments and illiberal regimes throughout the world, the Financial Times noted.