H.E Ambassador Grum Abay welcomes Ethiopian students  in Belgium

H.E Ambassador Grum Abay, Special Envoy, Extraordinary and Plenipotentiary of the FDRE to Belgium, Luxembourg and E.U. institutions, welcomed Ethiopian students in Belgium on Saturday, October 12/2019 at the Embassy premises.

The students from Vrije Universiteit Brussel, Université libre de Bruxelles, KU Leuven Université, Hasselt Université, Ghent Université and Université de Antwerp introduced themselves to the Ambassador and the staff of the embassy.

Briefings on the Hidase dam was given by H.E Ambassador Grum which resulted animated and open exchange of views on the issue. He also emphasized the need to join hands to counter attitudes that propagate our interest by being well equipped with updated information of our country.

On the Occasion, a short presentation was made by Ato Gebremichael Gebretsadik, Deputy Head of Mission on areas of collaboration with the students specifically regarding knowledge and technology transfer during their stay in the universities in Belgium.

After the discussion, it was agreed to work closely with the embassy by maintain strong connection among themselves. The ambassador, on the other hand, promised to support and provide efficient services to the students whenever needed.

The get together concluded by networking session and serving Ethiopian cultural food to those present.

ጠቅላይ ሚኒስትር ዓቢይ አህመድ የ2ዐ19 የሠላም ኖቤል ተሸላሚ መሆናቸውን በማስመልከት ክብርት ፕሬዝዳንት ሣህለ ወርቅ ዘውዴ ያስተላለፉት መልዕክት

ጠቅላይ ሚኒስትር ዓቢይ አህመድ የ2ዐ19 የሠላም ኖቤል ተሸላሚ መሆናቸውን በማስመልከት ክብርት ፕሬዝዳንት ሣህለ ወርቅ ዘውዴ ያስተላለፉት መልዕክት

በግለሰብም ሆነ በአንድ አገር ሕይወት ውስጥ የተለየ ቦታ የሚይዙ ቀኖች አሉ፡፡ የዛሬው ቀን ከእነዚህ መካከል አንደኛው ነው፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትራችን ክቡር ዶ/ር ዓቢይ አሕመድ የ2019 የኖቤል የሠላም ሽልማትን በማሸነፍ የመጀመሪያው ኢትዮጵያዊ ሆነዋል፡፡
በቅድሚያ በአገራችንና በውጭ አገራት በሚገኙ መላው ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያዊያን እንዲሁም በራሴ ስም እንኳን ደስ አሎት ለማለት እፈልጋለሁ፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትር ዓቢይ አህመድ ወደ ሥልጣን ከመጡ ጀምሮ ሰላም፣ ይቅርታና ፍቅርን ከማቀንቀን አቋርጠው አያውቁም፡፡ በሀገር ውስጥ የነበረውን አስፈሪ የፖለቲካ ፍጥጫ በማርገብ፣ በውጭ ሀገር የነበሩ የፖለቲካ ድርጅቶች ወደ ሀገር እንዲገቡ በማድረግ፣ ያለፈውን ታሪክ ዕሴቶች አስጠብቀን፣ ስህተቶችንም አርመን፣ አዳዲስ ዕሴቶችን በመጨመር የምንሄድበትን አካሄድ በመንደፍ፣ በኢትዮጵያና በኤርትራ መካከል የነበረውንና ሁለት አሥርተ ዓመታት ያስቆጠረውን ውጥረት በሠላም በመፍታት፣ ትላንት የተመረቀውን የአንድነት ፓርክ ዓይነት ያሉ የኢትዮጵያን ሥልጣኔ ወደፊት ሊወስዱ የሚችሉ አሻራዎችን ለትውልድ በመተው፣ በምሥራቅ አፍሪካ ቀጣና ትብብርን በማበረታታት፣ በጎረቤት ሀገሮችና በአገሮች መካከል የተፈጠሩ ችግሮችን ለመፍታት ቅድሚያውን በመውሰድ፣ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በዚህ በአጭር ጊዜ የሚቻላቸውን ሁሉ አድርገዋል፡፡
ዛሬ የተሸለሙት የኖቤል የሰላም ሽልማት ዋና ትርጉሙ ለእነዚህ ታላላቅ ሥራዎቻቸው ዓለም አቀፋዊ ዕውቅና መሰጠቱ ነው፡፡ ከዚያም ባሻገር ዓለም አቀፉ ሕብረተሰብ ኢትዮጵያ ላይ ያለውንም ተስፋ ያመላከተ ነው፡፡ ከሁሉም መአዘን እያስተጋባ ያለው የደስታ ስሜት እኛ ኢትዮጵያዊያን አንገታችንን በኩራት ከፍ እንድናደርግ የሚጋብዘን ነው፡፡ በእውነትም ልንኮራበት ይገባል፡፡
ኢትዮጵያውያን አንድ ሆነንና ተባብረን ሠርተን ያልተሳካልን ጊዜ የለም፡፡ ፉክክራችንን እርስ በርስ ማድረጋችንን ትተን ከዓለም ጋር ካደረግነው ማሸነፍ እንደምንችል ታሪክ በተደጋጋሚ ነግሮናል፡፡ አንድ ሆነን ቅኝ ገዥዎችን ታግለን ተሳክቶልናል፤ አፍሪካውያን ወንድሞቻችንና እህቶቻችን ነጻ እንዲወጡ አብረን ታግለን ተሳክቶልናል፤ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት እንዲመሠረት የምንችለው ሁሉ አድርገን ተሳክቶልናል፡፡ የአፍሪካ አንድነት ድርጅት እንዲመሠረት ታግለን ተሳክቶልናል፤
የምናተርፈው ከመለያየታችን ሳይሆን ከአንድነታችን፣ ከስንፍናችን ሳይሆን ከሥራችን መሆኑን አይተናል፡፡ በአንድ ዓመት ጊዜ ውስጥ ዓለምን የሚያስደንቅ ሥራ ሠርቶ በዓለም መድረክ ላይ መቆም እንደሚቻል የክቡር ጠቅላይ ሚኒስትሩ ሽልማት አሳይቶናል፡፡
እየተደማመጥን፣ እየተከባበርን የአገራችንን አንድነትና ጥቅም በማስቀደም ከዚህ በላይ ከሠራን ሥልጣኔያችንና ብልጽግናችን ራሱ ይሸልመናል፡፡ ሠላማችንና መረጋጋታችን ራሱ ይሸልመናል፡፡ የኢኮኖሚያችን ዕድገትና ዴሞክራሲያችን መጎልበት ራሱ ይሸልመናል፡፡
ከግራ ከቀኝ የሚወረወረውን እያሳለፉ፣ ፀንቶ መሥራት ምን ዋጋ እንዳለው የዛሬ ሽልማት ይነግረናል፤ እዚህም እዚያም በሚከሠቱ ተስፋ አስቆራጭ ነገሮች ሳይታወኩ ወደፊት እያዩ የአገርን ጥቅምና ታላቅነት በማስቀደም መሥራት እንዴት ያለ ክብር እንዳለው የዛሬው ሽልማት ያስተምረናል፡፡
ለኢትዮጵያ ታላቅነት ስንል፤ ችግሮቻችንን በውይይት ለመፍታት፣ ባንስማማም እንኳን ላለመስማማት ተስማምተን፣ በትንንሽ ምክንያቶች ሳንደናቀፍ፣ ሀገራችንን ብቻ አስቀድመን በርትተን እንሥራ፡፡ ይህ ከሆነ ከዚህ በላይ ገና ብዙ ድሎች ይቀሩናል፡፡
በድጋሚ ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር በኢትዮጵያ ሕዝብ ስም እንኳን ደስ ያለዎት

The 2019 Nobel Peace Prize has been awarded to Ethiopian Prime Minister Abiy Ahmed

Congratulations!!!

Ethiopian PM wins the Nobel Peace Prize 2019.

We are proud as a nation!!!

 

The Nobel Prize has been awarded “for his efforts to achieve peace and international cooperation, and in particular for his decisive initiative to resolve the border conflict with neighboring Eritrea”

The 2019 Nobel Peace Prize has been awarded to Ethiopian Prime Minister Abiy Ahmed.

He was awarded the prize for his efforts to “achieve peace and international cooperation”.

Ethiopia reached a peace deal with Eritrea last year, ending a 20-year military stalemate following their 1998-2000 border war.

He was named as the winner of the 100th Nobel Peace Prize in Oslo, where he will receive the award in December.

It is worth some nine million Swedish crowns (about £730,000; $900,000).

A total of 301 candidates had been nominated for the prestigious award, including 223 individuals and 78 organisations.

There had been great speculation over who would win the prize, with climate activist Greta Thunberg widely tipped as the favourite. Under the Nobel Foundation’s rules, nomination shortlists are not allowed to be published for 50 years.
Media captionThe announcement was made by Chair of the Norwegian Nobel Committee, Berit Reiss-Andersen
Who is Abiy Ahmed?

After becoming prime minister in April 2018, Mr Abiy introduced massive liberalising reforms to Ethiopia, shaking up what was an extremely tightly controlled nation.

He freed thousands of opposition activists from jail and allowed exiled dissidents to return home. Most importantly, he signed a peace deal with Ethiopia’s neighbour Eritrea, ending a two-decade conflict.

But his reforms also lifted the lid on Ethiopia’s ethnic tensions, and the resulting violence forced some 2.5 million people from their homes.
Why did he win?

The Norwegian Nobel Committee said in a statement that Mr Abiy was awarded for his “decisive initiative to resolve the border conflict with neighbouring Eritrea.”

“The prize is also meant to recognise all the stakeholders working for peace and reconciliation in Ethiopia and in the East and Northeast African regions,” they said.

“Peace does not arise from the actions of one party alone. When Prime Minister Abiy reached out his hand, President Afwerki grasped it, and helped to formalise the peace process between the two countries. The Norwegian Nobel Committee hopes the peace agreement will help to bring about positive change for the entire populations of Ethiopia and Eritrea.”
Who are previous Nobel Peace Prize winners?

Former US President Barack Obama won the Nobel Peace Prize in 2009, for “his extraordinary efforts to strengthen international diplomacy and co-operation between peoples”.

Other notable Nobel Peace Prize winners include former US President Jimmy Carter (2002), child education activist Malala Yousafzai (shared 2014), the European Union (2012), the United Nations and its then-general-secretary, Kofi Annan, (shared 2001) and Saint Teresa of Calcutta (1979).

#NobelPrize2019 #Nobel #NobelPeacePrize2019

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ የ2019 የሰላም ኖቤል ሽልማትን አሸነፉ
********************
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ የ2019 የሰላም ኖቤል ሽልማትን አሸንፈዋል፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትሩ የኖቤል ሽልማትን በማሸነፋቸው 9 መቶ ሺህ የአሜሪካን ዶላር ወይም 9 ሚሊዮን የስዊድን ክሮነር ይበረከትላቸዋል፡፡

ዘንድሮ ለዘርፉ ከቀረቡ እጩዎች መካከል ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድና የ16 ዓመቷ ስዊድናዊት የአየር ንብረት ለውጥ ተሟጋች ግሪታ ተንበርግ በሰፊው ያሸንፋሉ የሚል ግምት ተሰጥቷቸው ነበር፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ከ20 ዓመት በፊት ደም አፋሳሽ የነበረውንና በርካታ ሰዎች ያለቁበትን የኢትዮ- ኤርትራ ጦርነት መቋጫ እንዲያገኝ አድርገው ሰላም በማውረዳቸውና ምስራቅ አፍሪካ የትብብር ቀጠና እንዲሆን ያደረጉት ድፕሎማሲያዊ ጥረት የኖቤል ሽልማቱን እንዲያሸንፉ ጉልህ ሚና ተጫውቷል ተብሏል፡፡

በተለይም ወደ ደም መፋሰስ እየገባች የነበረችው የሱዳን የፖለቲካ ኃይሎች ተደራድረው የስልጣን ክፍፍል በማድረግ ወደ ሰላም መመለሳቸውም ትልቅ ዋጋ የሚያሰጥ ስኬት ተደርጎም ተወስዷል፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ በአንድ ቀን 350 ሚሊዮን ችግኝ ማስተከላቸውና በእርሳቸው አመራር የካቢኔያቸውን ግማሹ በሴቶች እንዲያዝ ማድረጋቸውም አለም አቀፉ ማህበረሰብ ድጋፍ እንዲቸራቸው ያደረገ መሆኑን የፖለቲካ ጠበብቶች ግምታቸውን ሰጥተዋል፡፡

በተለያዩ መስኮች ጉልህ ተግባራቶችን ያከናወኑ ግለሰቦችን ተቋማት በየዓመቱ የሚሸለሙበት የኖቤል ሽልማት በአለማችን ከሚሰጡ ሽልማቶች መካከል ቀዳሚው ነው፡፡

እንደ ቢቢሲ መረጃ እ.ኤ.አ 1938 ንጉሰ ነገስት ቀዳማዊ አፄ ኃይለስላሴ ለኖቤል ሽልማት ታጭተው ነበር፡፡

Prime Minister Abiy Ahmed welcomed leaders of IGAD member states who are visiting Ethiopia for the inauguration of Unity Park

Prime Minister Abiy Ahmed welcomed leaders of IGAD member states, President Yoweri Museveni, President of the Republic of Uganda; President Uhuru Kenyatta of the Republic of Kenya, President Salva Kiir of the Republic of South Sudan; President Mohammed Abdulahi Mohammed of the Federal Republic of Somalia; Prime Minister Abdalla Hamdok of the Republic of Sudan and H.E. Nabil Mohamed Ahmed, Head of Delegation of the Republic of Djibouti, who are visiting Ethiopia for the inauguration of Unity Park within the Grand National Palace.

The Government of Ethiopia affirms its position to advance the trilateral technical dialogue concerning the filling and operation of the Grand Ethiopian Renaissance Dam

The Government of Ethiopia affirms its position to advance the trilateral technical dialogue concerning the filling and operation of the Grand Ethiopian Renaissance Dam.
The Water Affairs Ministers of Egypt, Ethiopia, and Sudan met in Khartoum on 04 and 05 October 2019. Prior to the Ministers’ meeting, the National Independent Scientific Research Group of the three countries met in Khartoum on 30 September – 03 October 2019.
The Government of Ethiopia is of the conviction that the technical consultation must continue, as it presents the only option for resolution of differences among the three countries with respect to filling and operation of the GERD. Although the unilateral proposal on technical aspects of filling and operation of the GERD by the Government of Egypt side-steps the working procedure of the NISRG and disrupted the ongoing process, the Water Affairs Ministers in their meeting in Cairo on 15 and 16 September 2019 instructed the NISRG to discuss and analyze the filling and operation plan of Ethiopia and the submissions of Egypt and Sudan on technical aspects of filling and operation.
Based on the direction given by the Water Affairs Ministers meeting in Cairo, the NISRG considered Ethiopia’s filling and operation plan of the GERD, and the proposals of Egypt and the Sudan. The deliberation of the Scientific Research Group was based on an outline adopted by consensus between the three country teams. The Group reached an agreement on some points while some other issues remain outstanding. These points of divergence could be resolved through further deliberation by the NISRG.
The filling plan of Ethiopia that is set to be completed in stages that will take four to seven years based on the hydrology is considerate of the interests of the downstream countries of the Nile. Furthermore, Ethiopia and Sudan followed a constructive and inclusive approach for the discussion of the NISRG. Whereas, the Egyptian Side persisted on its position of having all its proposals accepted without which it was not willing to have the NISRG conduct its analysis.
This approach by the Government of Egypt is not new. Rather, it is yet another instance of a disruptive tactic it applied to halt the hydrology, environmental and social impact assessment on the GERD. Ethiopia maintains its stand on the possibility of resolving the issues based on trilateral technical consultation and the invocation of principle X of the DOP is premature.
Despite the tireless efforts of the Ministers of Water Affairs, during their two days meeting to consider the progress of the work of the NISRG, they did not manage to put a direction on the way forward due to the predetermined plan of the delegation of Egypt to make the process fail.
The proposal by the Government of Egypt to invite third party in the discussions is an unwarranted denial of the progress in the trilateral technical dialogue and violates the Agreement on the Declaration of Principles signed by the three countries on 23 March 2015. It also goes against the consent and wishes of Ethiopia and the Sudan; it negatively affects the sustainable cooperation between the Parties; undermines the ample opportunity for technical dialogue between the three countries; and disrupts the positive spirit of cooperation.
Additionally, the proposal to subject the discussion on filling and operation of the GERD to a political forum is unjustified by the nature of the outstanding technical issues. It also contravenes the direction given by the leaders of the three countries given to the Water Affairs Ministers to resolve the technical issues related to filling and operation of the Dam, it will also not allow attainment of a successful resolution of the technical issues.
The Government of Ethiopia believes the existing mechanisms of cooperation will allow resolution of differences and reminds the need to refrain from negative media and other campaigns that will have no other effect than eroding the confidence among the three countries.
The Government of Ethiopia will reinforce its efforts to realize development of its water resource to meet the present and future needs of its people that deserve development and adequate standard of living.
Ethiopia upholds the principles of equitable and reasonable utilization and the causing of no significant harm on any other riparian country in the use of the waters of the Nile. Furthermore, the Government of Ethiopia will continue to follow an approach that will not result in direct or indirect recognition of any preexisting water allocation treaty, which has no applicability whatsoever on Ethiopia.

#MoFA

የኢትዮጵያ መንግስት በታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የውሃ አሞላል እና አለቃቀቅ ዙሪያ የተጀመረውን የሶስትዮሽ ቴክኒካዊ ምክክር ለማስቀጠል ቁርጠኛ ነው

የኢትዮጵያ መንግስት በታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የውሃ አሞላል እና አለቃቀቅ ዙሪያ የተጀመረውን የሶስትዮሽ ቴክኒካዊ ምክክር ለማስቀጠል ቁርጠኛ ነው::

የግብጽ፣ ኢትዮጵያ እና ሱዳን የውሀ ጉዳይ ሚኒስትሮች መስከረም 5 እና 6 ቀን 2012 ዓ.ም በካይሮ ባካሄዱት ስብሰባ ባስቀመጡት የጊዜ ሰሌዳ መሰረት በካርቱም የሶስትዮሽ ስብሰባቸውን አካሂደዋል፡፡ ከሚኒስትሮቹ ስብሰባ አስቀድሞ የአገራቱ ገለልተኛ የሳይንሳዊ ጥናት ቡድን ከመስከረም 19 እስከ 22 ቀን 2012 ዓ.ም በካርቱም አምስተኛ ዙር ስብሰባውን አካሂዶ በታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ሙሌት እና የውሃ አለቃቅ ቴክኒካዊ ጉዳዮች ዙሪያ መክሯል፡፡

የኢትዮጵያ መንግስት በአገራቱ መካከል የሚደረገው ቴክኒካዊ ምክክር ብቸኛው የመፍትሄ አማራጭ በመሆኑ መቀጠል እንደሚኖርበት ያምናል፡፡
የሳይንሳዊ ቡድኑ አራት ስብሰባዎችን አድርጎ አበረታች ውጤት እያሳየ ባለበት ወቅት ግብጽ በተናጠል ያቀረበችው የውሃ ሙሌት እና አለቃቀቅን የሚመለከተው ሰነድ ከትብብር ማዕቀፉ ውጪ የሆነ እና ሂደቱን ያናጠበ ሆኗል፡፡ ሆኖም የውሃ ሚኒስትሮች የኢትዮጵያ የውሃ ሙሌት እና አለቃቀቅ እቅድ፣ የግብጽ መንግስት የሚያቀርበው ሰነድ እንዲሁም ሱዳን በጉዳዩ ላይ የምታቀርበው ሰነድ ለሳይንሳዊ ቡድኑ ቀርቦ ዝርዝር ትንታኔ እንዲደረግበት እና ምክረ ሃሳብ እንዲቀርብለት በመስከረም ወር 2012 ዓ.ም በካይሮ በተደረገው ስብሰባ ወስነዋል፡፡

በካርቱም አራት ቀናትን ወስዶ በተካሄደው ስብሰባ የሳይንሳዊ ቡድኑ በመስከረም ወሩ የካይሮ ስብሰባ በተሰጠው አቅጣጫ መሠረት የኢትዮጵያን የግድብ ሙሌት እና የውሃ አለቃቅ ዕቅድ፣ እንዲሁም ሱዳን እና ግብጽ ያቀረቡትን የሙሌት እና የውሃ አለቃቅ ቴክኒካዊ ጉዳዮችን የሚዳስሰውን ሃሳብ አዳምጦ ውይይቶችን አካሂዷል፡፡ ውይይቱ ሶስቱም ቡድኖች በተስማሙበት የርዕሰ ጉዳይ መዘርዝር ላይ የተመሰረተ ሲሆን በአንዳንድ ጉዳዮች ላይ ከመስማማት ተደርሶ በሌሎቹ ላይ የሃሳብ መለያየቶች ተመዝግበዋል፡፡

እነዚህ የሃሳብ ልዩነቶች በሳይንሳዊ እና ጥናት ቡድኑ ውይይት እና ትንተና መግባባት ሊደረስባቸው የሚችሉ ናቸው፡፡
ኢትዮጵያ ግድቡን እሰከ ሰባት አመት ድረስ በሚወስድ ሂደት ለመሙላት ያቀረበችው እቅድ የታችኛውን ተፋሰስ አገራት ጥቅም ለመጠበቅ ያላትን አቋም ያሳያል፡፡ ይህም በተጨማሪም ኢትዮጵያ እና ሱዳን ማናቸውም ቱክኒካዊ ጉዳዮች ለሳይንሳዊ ጥናት ቡድኑ ቀርበው ትንተና እንዲደረግባቸው ገንቢ እና አካታች የውይይት አካሄድ ቢከተሉም የግብጽ ወገን ያቀረብኳቸው ሃሳቦች በሙሉ ተቀባይነት ካላገኙ ውይይቱ ሊቀጥል አይችልም በሚለው የማያሰራ አቋሙ በመቀጠሉ የሳይንሳዊ ጥናት ቡድኑ ስራውን በተሟላ አኳኋን ማከናወን ሳይችል ቀርቷል፡፡ ይህ የግብጽ አቋም የሳይንሳዊ ጥናት ቡድኑ ስብሰባ እንዲሁም የሚኒስትሮች ስብሰባው ስምምነት በተደረሰባቸው ጉዳዮች ላይ ጭምር ሪፖርት እንዳያዘጋጁ አድርጓል፡፡
ይህ የግብጽ አካሄድ አዲስ ሳይሆን ከዚህ ቀደምም በግድቡ ላይ ሶስቱ አገራት ሊያከናውኑት የነበረውን የውሃ፣ የአካባቢያዊ እና ማህበራዊ ተጽእኖ ጥናት በግብጽ ወገን እንዲስተጓጎል በተደረገ ጊዜ የታየ የሳይንስ እና የምክክር የመፍትሄ አማራጭን የማፋለስ ዘዴ ነው፡፡
ኢትዮጵያ አለመግባባት መፍቻ ዘዴን የሚደነግገውን የመርህ መግለጫ ስምምነቱን አንቀጽ 10 ጠቅሶ መፍትሄ ለመፈለግ ጊዜው እንዳልሆነ እና ቴክኒካዊ ምክክሩ ሊቀጥል እንደሚገባ ታምናለች፡፡
የውሃ ሚኒስትሮቹ በሁለት ቀናት ስብሰባቸው የሳይንሳዊ ጥናት ቡድኑ የደረሰበትን ተመልክተው አቅጣጫ ለማስቀመጥ ከፍተኛ ጥረት ቢያደርጉም የግብጽ ወገን ቀድሞውኑ የምክክር ሂደቱ እንዲፋረስ አቋም ይዞ የመጣ በመሆኑ ጉባኤው የሳይንሳዊ ጥናት ቡድኑ በቀጣይነት ማከናወን ስላለበት ተግባር መመሪያ ሳያስተላልፍ ቀርቷል፡፡
የግብጽ መንግስት ሶስተኛ ወገን በጉዳዩ ጣልቃ እንዲገባ እያቀረበ ያለው ሃሳብ በሶስቱ አገራት የትብብር መድረክ የታየውን አበረታች ሂደት የሚያጣጥል እና ሶስቱም አገራት በመጋቢት 2007 ዓ.ም. የፈረሙትን የመርሆዎች መግለጫ ስምምነት የሚጥስ ተግባር ነው፡፡ የሶስተኛ ወገን ጣልቃ-ገብነት ኢትዮጵያ እና ሱዳን የማይቀበሉት እና ተገቢ ያልሆነ፤ በአገራቱ መካከል ያለውን ዘላቂ ትብብር የሚጎዳ፤ ለውይይት ያለውን በቂ እድል ወደጎን የሚያደርግ እና ገንቢ የሆነውን የውይይት መንፈስ የሚያደፈርስ ነው፡፡
ቴክኒካዊ ምክክር የሚጠይቀው የግድብ ሙሌት እና ውሃ አለቃቀቅ ጉዳይ ለፖለቲካ ምክክር እንዲቀርብ የሚጠይቀው ሃሳብም የጉዳዩን ጠባይ ያላገናዘበ፣ የሶስቱ አገራት መሪዎች የውሃ ጉዳይ ሚኒስትሮች ጉዳዩን ለመፍታት የሰጡትን መመሪያ የጣሰ እንዲሁም ተገቢ መፍትሄ ለመስጠት የማያስችልም ነው፡፡
የኢትዮጵያ መንግስት ልዩነቶችን ለመፍታት እድል የሚፈጥረውን የምክክር ሂደት ለማጠናከር እንደሚሰራ እየገለጸ በጉዳዩ ላይ የሚሰራጨው የመገናኛ ብዙሃን እንዲሁም ሌላ አሉታዊ ዘመቻ የሶስቱን አገራት መተማመን ከመሸርሸር ያለፈ ውጤት እንደማይኖረው ይገልጻል፡፡

የኢትዮጵያ መንግስት በተደጋጋሚ እንደገለጸው የአባይን ውሃ የኢትዮጵያ ህዝቦችን የአሁን እና የወደፊት ፍላጎት ለማሟላት እና ብሄራዊ ጥቅምን ለማረጋገጥ ማልማቱን በመቀጠል ርትዕን የጠበቀ እና በማናቸውም የተፋሰሱ አገራት ላይ ጉልህ ጉዳት የማያደርስ አጠቃቀም እንዲኖር ይሰራል፡፡

በተጨማሪ የኢትዮጵያ መንግስት በሕዳሴ ግድብ ላይ በሚደረገው ውይይት የሚከተለው አቅጣጫ የናይል ውሃን አስመልክቶ ለተደረጉት እና በኢትዮጵያ ላይ ምንም አይነት ተፈጻሚነት የሌላቸውን ስምምነቶች እውቅና የማይሰጥ እንዲሁም የላይኛውን የናይል ተፋሰስ አገራት መብት የማይጥስ እንዲሆን ነው::

MoFA