ከኦገስት 18 እስከ 22 ቀን 2025 ዓ.ም. በቤልጅየም ፍሌሚሽ እና በኢትዮጵያ ዩኒቨርስቲዎች የድህረ-ምረቃ (PhD) ልምድ ልውውጥ ወርክሾፕ የተሳተፉ ከሰባት የኢትዮጵያ ዩኒቨርስቲዎች የተወጣጡ ምሁራን በብራሰልስ የኢ.ፌ.ዲ.ሪ. ኤምባሲ በመገኘት ከክቡር አምባሳደር እሸቴ ጥላሁን ጋር ስለቆይታቸው ሃሳብ ተለዋውጠዋል።

ከኦገስት 18 እስከ 22 ቀን 2025 ዓ.ም. በቤልጅየም ፍሌሚሽ እና በኢትዮጵያ ዩኒቨርስቲዎች የድህረ-ምረቃ (PhD) ልምድ ልውውጥ ወርክሾፕ የተሳተፉ ከሰባት የኢትዮጵያ ዩኒቨርስቲዎች የተወጣጡ ምሁራን በብራሰልስ የኢ.ፌ.ዲ.ሪ. ኤምባሲ በመገኘት ከክቡር አምባሳደር እሸቴ ጥላሁን ጋር ስለቆይታቸው ሃሳብ ተለዋውጠዋል።
አምባሳደር እሸቴ በመጪው አመት በሚከበረው የኢትዮጵያና ቤልጅየም የዲፕሎማሲ ግንኙነት 120ኛ ዓመት ክብረ- በዓል የትምህርት ዘርፍ ትብብርን መዘከር እንደሚገባና ክብረ-በዓሉ ትብብሩን በሚያሳይ መልኩ መከበር እንዳለበት አንስተዋል። ከትብብሩ የተገኘውን ልምድ ወደሁሉም ዩኒቨርሲቲዎቻችን ማስፋት ጠቃሚ መሆኑን የሁለቱ ወገን የፕሮግራም አስተባባሪዎች ገልፀዋል።
Professors from seven Ethiopian Universities who took part in the Flemish–Ethiopian Postgraduate (PhD) Experience sharing Workshop, held from August 18 to 22, 2025, visited the Embassy of the Federal Democratic Republic of Ethiopia in Brussels. The Professors and engaged in discussions with H.E. Ambassador Eshete Tilahun to reflect impression of their mission.
Ambassador Eshete emphasized the importance of further strengthening the cooperation in the higher education and of showcasing such collaboration as part of the upcoming celebration of the 120th Anniversary of Ethiopia–Belgium diplomatic relations. Coordinators of the programmers for both sides emphasized the importance of scaling up the Doctoral Degree Programs.

በቤኔሉክስ ለሚገኙ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ- ኢትዮጵያውያን ልጆች ለኢትዮጵያ ያላቸውን ፍቅር ለማነቃቃት እንዲሁም ባህልና እሴትን እንዲያውቁ ለማድረግ ያለመ ከእለታት አንድ ቀን……. በኢትዮጵያ ቤት ልዩ የልጆች መዝናኛ ዝግጅት ብራሰልስ በሚገኘው የኢ.ፌ.ዲ.ሪ. ኤምባሲ ዛሬ ነሐሴ 10 ቀን 2017 ዓ.ም. በድምቀት ተከናውኗል።

በቤኔሉክስ ለሚገኙ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ- ኢትዮጵያውያን ልጆች ለኢትዮጵያ ያላቸውን ፍቅር ለማነቃቃት እንዲሁም ባህልና እሴትን እንዲያውቁ ለማድረግ ያለመ ከእለታት አንድ ቀን……. በኢትዮጵያ ቤት ልዩ የልጆች መዝናኛ ዝግጅት ብራሰልስ በሚገኘው የኢ.ፌ.ዲ.ሪ. ኤምባሲ ዛሬ ነሐሴ 10 ቀን 2017 ዓ.ም. በድምቀት ተከናውኗል።
በዝግጅቱ ክቡር አምባሳደር እሸቴ ጥላሁን ባስተላለፉት መልዕክት ልጆች ከምንጫቸው ጋር ትስስር እንዲፈጥሩ ወላጆች ሚና እንዳላቸው አንስተው፣ ዳያስፖራው በሚገኝበት ማህበረሰብ እርስበርስ መተዋወቅ፣ መተሳሰር እንዲሁም ለአገር አንድነት በጋራ መስራት አስፈላጊ መሆኑን ገልፀዋል።
በሉግዘምበርግ የኢትዮጵያ የክብር ቆንስል እና የላሜ ቦራ (ፈረንሳይኛ) ጸሃፊ ማዳም ሄኖኬ ወልደመድህን ኩርት በዝግጅቱ ባስተላለፉት መልዕክት ዳያስፖራው ለልጆች የኢትዮጵያን ባህልና እሴት በማስተማር ማሳወቅ እንዳለበትና የበለጸገ ታሪክ ባላት ኢትዮጵያ መኩራት እንደሚገባ ገልፀዋል። ከአገራችን እውቅ የልጆች ታሪኮች አንዱ የሆነውን ” ላሜ ቦራ” የተረት መፅሃፍ በፈረንሳይኛ የፃፉበትን መሰረት ሃሳብ በማብራራት ታሪኩ አንብበዋል።
በቤልጅየም ለማህበራዊ አገልግሎት የመጡት አርቲስት ንብረት ገላው ( እከ) በዝግጅቱ በመገኘት ስለ አገር ፍቅርና በጋራ ስለመስራት አስፈላጊነት ንግግር አድርገዋል። በዝግጅቱ ከተገኙ ልጆች ጋር የቡሄ ጭፈራን እንዲሁም ሌሎች ባህላዊ ጨዋታዎችን በማስተዋወቅ ታዳሚ ልጆች ባህሉን እንዲረዱ አድርገዋል።
በእለቱ ከተረት ንባብ በተጨማሪ ልጆች የራሳቸውን ሃሳብ የሚያመነጩ የሥነ-ጥበብ ስራዎችን እንዲለማመዱ ትስስር እንዲፈጥሩ ተደርጓል።

ክቡር አምባሳደር እሸቴ ጥላሁን በኔዘርላንድ ሮተርዳም ከተማና አካባቢው ከሚኖሩ የሶማሌ ኮሚዩኒቲ አባላት ጋር ተወያዩ፣

ክቡር አምባሳደር እሸቴ ጥላሁን በኔዘርላንድ ሮተርዳም ከተማና አካባቢው ከሚኖሩ የሶማሌ ኮሚዩኒቲ አባላት ጋር ተወያዩ፣
ክቡር አምባሳደር እሸቴ ጥላሁን በኔዘርላንድ ሮተርዳም ከተማና አካባቢው ከሚኖሩ ኢትዮጵያዊና ትውልደ ኢትዮጵያዊያን የሶማሌ ኮሚዩኒቲ አባላት ጋር ዛሬ ነሃሴ 4 ቀን 2017 ዓ.ም. ተወያይተዋል። ውይይቱ በአገራዊ ሰላምና ዲሞክራሲ ግንባታ፣ በኢንቨስትመንት፣ ንግድና የልማት ተሳትፎ ያተኮረ ነበር።
በመድረኩ በመልካም አስተዳደር፣ በልማትና በአገራችን ወቅታዊ ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ማህበራዊ ጉዳዮች ከኮሚዩኒቲው ለተነሱ ጥያቄዎች እና አስተያየቶች ክቡር አምባሳደር እሸቴ ገለፃ የሰጡ ሲሆን ዳያስፖራው ለአገራዊ ልማት ተሳትፎውን አጠናክሮ እንዲቀጥል ጥሪ አቅርበዋል።
ኢትዮጵያዊና ትውልደ-ኢትዮጵያዊ የሶማሌ ኮሚዩኒቲ አባላት የዳያስፖራውን ችግሮች በማቃለል ረገድ ሚሲዮኑ ለሚያደርገው ድጋፍ አመስግነው፣ ለታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ማጠናቀቂያ የቦንድ ግዢ እና የስጦታ ድጋፍ አድርገዋል። ለአገር አንድነትና ልማት የሚያደርጉትን አስተዋጽኦ እንደሚያስቀጥሉም ቃል ገብተዋል።
በመድረኩ ለክቡር አምባሳደር እሸቴ ጥላሁን እና ኮሚኒቲውን ላጠናከሩ የዳያስፖራ አባላት ስጦታ እና የምስክር ወረቀት ተበርክቶላቸዋል። በተጨማሪም ኬክ የመቁረስ ስነ-ስርዓት ተከናውኖ በድምቀት ተጠናቋል።
H.E. Ambassador Eshete Tilahun Engages with Ethiopian and Ethiopian-Origin Somali Diaspora in Rotterdam
Rotterdam, Netherlands – On 10 August 2025, H.E. Ambassador Eshete Tilahun held a fruitful discussion with members of the Ethiopian and Ethiopian-origin Somali diaspora community. The meeting focused on strengthening national development, investment, and trade, while also addressing good governance and Ethiopia’s political, economic, and social affairs.
The community expressed strong support for the Grand Ethiopian Renaissance Dam (GERD) through bond purchases and donations, reaffirming their commitment to the national flagship project. They also conveyed appreciation to the Embassy for its continued support and pledged to contribute further to Ethiopia’s unity and prosperity.
The event concluded with a vibrant ceremony, featuring the awarding of certificates to Ambassador Eshete Tilahun and diaspora members in recognition of their contributions to community strengthening.

ከእለታት አንድ ቀን በኢትዮጵያ ቤት

ከእለታት አንድ ቀን ……….. በኢትዮጵያ ቤት

የማይቀርበት ልዩ የልጆች የመዝናኛ ዝግጅት በኢ.ፌ.ዲ.ሪ. ኤምባሲ ብራሰልስ ተዘጋጅቶላችኋል።

መቼ- ነሐሴ 10 ቀን 2017 ዓ.ም (August 16,2025) ከቀኑ 14፡00 እስከ 16፡00 ሰዓት

ምን አለ? በቤኔሉክስ ለሚገኙ ኢትዮጵያውያን እና ትውልደ- ኢትዮጵያውያን ልጆች ለኢትዮጵያ ያላቸውን ፍቅር ለማነቃቃት፣ ባህልና እሴትን እንዲያውቁ ለማድረግ፣ የልጆችን የፈጠራ ችሎታ በመጠቀም ለክረምት የበጎ ፈቃድ ፕሮግራም ድጋፍ ለማሰባሰብ “ትንሽ እጅ ትልቅ ልብ” በሚል መሪ ሃሳብ ይህ ፕሮግራም ተዘጋጅቷል።
ልጆችዎ የኢትዮጵያን ባህላዊ ጨዋታዎች ይታደማሉ፣ ከታዋቂው ኢትዮጵያዊ አርቲስት ንብረት ገላው (እከ ደከ) ጋር ይተዋወቃሉ፣ በፈረንሳይኛ ቋንቋ የተዘጋጀውን “ላሜ ቦራ” መፅሃፍ በጸሐፊ ማዳም ሄኖኬ ኮርቴ ይነበባል፣ ለክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት ልጆችዎ የበኩላቸውን ያበረክታሉ።

*ለመመዝገብ diaspora.brussels@mfa.gov.et ወይም ‪+32 495 133 346‬ ላይ መልዕክት ያስቀምጡ
የት? Avenue de Tervuren 64 1040 Etterbeek, The Embassy of Ethiopia in Brussels

Ambassador Eshete Tilahun Highlights Heritage Cooperation at African Collections Workshop

Ambassador Eshete Tilahun Highlights Heritage Cooperation at African Collections Workshop
Bahir Dar/Brussels, 30 July 2025- H.E. Ambassador Eshete Tilahun delivered remarks at the “Workshop on the Ethics of Curating African Collections,” co-organized by the Africa Museum (Belgium) and Bahir-Dar University Museum Project (Ethiopia). Addressing curators, scholars, and heritage professionals, Ambassador Eshete emphasized the critical role of ethics, restitution, and international collaboration in preserving Africa’s cultural legacy.
The Ambassador commended the joint efforts between Belgian and Ethiopian institutions, calling them a model for future partnerships. He accent Ethiopia’s longstanding diplomatic ties with Belgium, dating back to 1906, and pointed to upcoming cultural events, including the proposed exhibition “High Voltage and Highlights: Ethiopia and Belgium.”
He highlighted Ethiopia’s robust legal framework for heritage protection, its engagement in international conventions like UNESCO’s 1970 treaty, and recent successful restitution efforts, including the return of sacred and royal artifacts from the United Kingdom.
Ambassador Eshete also called on curators not only to preserve but to actively help restore Africa’s looted heritage, and to amplify African narratives globally. He urged further action in four key areas: deepening Ethiopia-Belgium heritage collaboration, elevating the historical significance of artifacts, strengthening legal frameworks, and raising up public understanding and systemic ownership of cultural heritage.
Ethiopian Art Conservation Program

H.E. Ambassador Eshete Tilahun and his team conferred with representatives of Waste Management and Mining Companies Representatives Ambassador Eshete Tilahun discussed with Mr. Lieven Claus and his team, representatives of Waste Management and Mining Companies, on 28 July 2025.

H.E. Ambassador Eshete Tilahun and his team conferred with representatives of Waste Management and Mining Companies Representatives
Ambassador Eshete Tilahun discussed with Mr. Lieven Claus and his team, representatives of Waste Management and Mining Companies, on 28 July 2025.
The representatives explained about the growing importance of the Waste Management Industry, which is even more vital for big and populous countries like Ethiopia. They also expressed their willingness to work with Ethiopian partners.
Ambassador Eshete, on his part, presented to the representatives the existing demands for investments in the Waste Management and Mining Sectors of Ethiopia. He assured the representatives the Embassy’s readiness to facilitate business ties with Ethiopia.